Tora ቶራ

Tora ቶራ Marketing, sales,

✝️✝️ዓርብ ~ ቤተክርስቲያን ✍️ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል በዘይቤያዊ ፍቺ ሦስት ዓይነት ትርጉም አለው።            ይህም፦፩ኛ,  የክርስቲያን ቤት የክርስቲያን መሰብሰቢያ ማለት ነው...
17/04/2026

✝️✝️ዓርብ ~ ቤተክርስቲያን

✍️ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል በዘይቤያዊ ፍቺ ሦስት ዓይነት ትርጉም አለው።
ይህም፦
፩ኛ, የክርስቲያን ቤት የክርስቲያን መሰብሰቢያ ማለት ነው። ይህም ማለት ክርስቲያኖች በአንድነት በመሰብሰብ ሥርዓተ አምልኮትን የሚፈጽሙበት ቦታ መሆኑን ያመለክታል። (ኢሳ ፶፮፥፯ ፣ ኤር ፯፥፲-፲፩ ፣ ማቴ ፳፩፥፳፫ ፣ ማር ፲፩፥፲፯ ፣ ሉቃ ፲፱፥፵፱)

፪ኛ, የክርስቲያኖች ስብስብ የክርስቲያኖች አንድነት ማለት ሲሆን "ቤተ እስራኤል ፣ ቤተ ያዕቆብ ፣ ቤተ አሮን" ሲል የእስራኤል ወገን፣ የያዕቆብ ወገን፣ የአሮን ወገን ማለት እንደሆነ ሁሉ ቤተክርስቲያን ሲባልም የክርስቲያን ወገን ማለት ነው። (መዝ ፻፲፯፥፫ ፣ ማቴ ፲፮፥፲፰ ፣ ማቴ ፲፰፥ ፲፯ ፣ ራእ፩፥፲፩)

፫ኛ, እያንዳንዱ ክርስቲያን ቤተክርስቲያን ይባላል። ይህም ቤተመቅደስ (ቤተክርስቶስ) ለማለት ነው።(፩ኛ ቆሮ ፫፥፲፮፣፲፮፥፲፮ ፣ ፪ኛ ቆሮ ፮፥፲፮)
በአጠቃላይ አነጋገር የቤተክርስቲያን ሥርዓት ሲባል የክርስቲያኖች ሕግ ፣ ቀኖና አሠራር ማለት ነው።

✔️ታዲያ ጌታችን በተነሣ በስድስተኛው ቀን ቤተክርስቲያን ተብሎ መከበሩ ጌታችን በመስቀል ተሰቅሎ ደሙን አፍሶ ቤተክርስቲያንን የመሠረተ መሆኑን ለማሰብ ነው።
✍️ለዚህም መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ነው። "ወይእዜኒ ዕቀቡ ርእሰክሙ ወኵሎ መራዕየ ዘሎቱ ሤመክሙ መንፈስ ቅዱስ ጳጳሳተ ከመ ትርዐዩ ቤተ ክርስቲያኑ ለእግዚአብሔር እንተ አጥረያ በደሙ "
🔐ትርጉም
"አሁንም በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ"(ሐዋ፳፥፳፰) የሚለውና ሌላውም ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስ አማናዊ ቃል ነው።

✍️ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማዕከለ ምድር በቀራንዮ ሲሰቀል ከተወጋው ጎኑ የፈሰሰውን ክቡር ደም መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በብርሃን ጽዋዕ ቀድቶ በዓለም ነዝቶት/ረጭቶት ነበርና ደሙ በነጠበበት ሁሉ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ቤተክርስቲያን ስትሠራ ትኖራለች። ድርሳነ ዑራኤል ገጽ ፻፶፰ ቁጥር ፳፪ ይመልከቱ።

💐ሐሙስ   አዳም💐     ጸውዖ እግዚኡ ለአዳም ወይቤሎ ነዓ ፃዕ ምስለ ነፍሰ ጻድቃን በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን ይቤሎ እግዚኡ ለአዳም አዳም አዳም አበ ኲሉ ዓለም ፤                  ...
16/04/2026

💐ሐሙስ አዳም💐

ጸውዖ እግዚኡ ለአዳም ወይቤሎ ነዓ ፃዕ ምስለ ነፍሰ ጻድቃን በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን ይቤሎ እግዚኡ ለአዳም አዳም አዳም አበ ኲሉ ዓለም ፤
{ትርጉም}
ጌታውና ፈጣሪ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን የዓለሙ ሁሉ አባት አዳም አዳም በጽኑ ኃይልና ሥልጣን ከጻድቃን ነፍስ ጋራ ከሲኦል ና ውጣ ብሎ አዳምን ጠራው። ቅ. ያሬድ

➢አዳም የመጀመሪያ ሰውና የሰው ሁሉ አባት ነው።
በ፮ኛው ቀን የተፈጠረ የሰው ሁሉ ምንጭ ስለሆነ የሰው ዘር ሁሉ ከእርሱ ተገኝቷል። ዘፍ ፩፥ ፳፮
አዳምና ሔዋን በገነት ፯ ዓመት ከቆዩ በኋላ ትእዛዙን በመተላለፋቸው ከኤደን ገነት
አስወጣቸው። ኩፋ.፬፥፲፮ ዘፍ .፫፥፳፫
ብዙ ተባዙ ያለው ቃል እንዳይቀር በምድር ላይ ወርደው ልጆችን ወለዱ ይላል፡፡
የተወለዱትም ልጆችም በቁጥር ፷ እንደሆኑ
በ፩ኛ መቃ. ፳፰፥፮ ተጽፏል።
የተወለዱት ልጆች ደጎችና ክፉዎች እንደ ነበሩ በአቤልና በቃየል ታውቋል።
●ዘፍ. ፬፥፰
አዳም በዚህ ዓለም ፱፻፴ ዓመት ኑሮ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ፵፻፭፻፸ ሚያዝያ ፮ አርፏል፡፡
ይህ ዕለት አዳም ከነልጆቹ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻ መውጣቱ ይታሰብበታል፡፡

ጌታችን አዳምን ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ብሎ ቃል ገብቶለት እንደ ነበር በቀሌምንጦስ ተጽፏል ፡፡
ክርስቶስ በተነሣበት በአምስተኛው ቀን
ሐሙስ በዓሉ እንዲከበር ተወስኗል ዕለቱም የአዳም ሐሙስ ተብሏል ።
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤
በዐቢይኀይል ወሥልጣን፤
አሰሮ ለሰይጣን፤
አግዓዞ ለአዳም፤
ሰላም፤
እምይእዜሰ፤
ኮነ
ፍሥሐ ወሰላም።

15/04/2026
የአልዓዛር ረበዕ(ነአምን በዘአንሥኦ ለአልዓዛር እመቃብር ወኪያነሂ ያነሥአነ ምስሌሁ በትንሣኤሁ እምነ ሙታን።)እኛን በትንሣኤው ከሙታን ለይቶ ከራሱ ጋራ ያስነሣናልና፤አልዓዛርን ከመቃብር ባስነ...
15/04/2026

የአልዓዛር ረበዕ

(ነአምን በዘአንሥኦ ለአልዓዛር እመቃብር ወኪያነሂ ያነሥአነ ምስሌሁ በትንሣኤሁ እምነ ሙታን።)
እኛን በትንሣኤው ከሙታን ለይቶ ከራሱ ጋራ ያስነሣናልና፤
አልዓዛርን ከመቃብር ባስነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን ቅ ያሬድ

ክርስቶስ ከሙት ያስነሳው አልዓዛር የማርያምና የማርታ ወንድም ነው።
የስሙም ትርጓሜ እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው ።

ዮሐ. ፲፩፥፯-፵፰
አልዓዛር የሞተው መጋቢት ፲፯ ረቡዕ ቀን ነው።
አልዓዛር በሞተ ጊዜ እኅቶቹም ክርስቶስ እንዲመጣ መልእክት ልከውበት ነበር። ክርስቶስ ግን በ፬ኛው ቀን ማለትም መጋቢት ፳ ቅዳሜ ቀን መጥቶ ከሞት አስነሥቶታል።
ዮሐ.፲፩፥፵፬
ክርስቶስ ፋሲካውንም በወዳጁ በአልዓዛር ቤት ያከብር ዘንድ ደቀ- መዛሙርቱ ጴጥሮስንና ዮሐንስን አስቀድሞ ላከ፤ ከዚያም በአልዓዛር ቤት ሆኖ የሐዲስ ኪዳንን ሥርዓት ምሥጢረ ቁርባንን ሠርቶ ለደቀ መዛሙርቱ አሳያቸው፤ አልዓዛር ከተነሣ በኋላ በሐዋርያት ኤጲስ ቆጶስነት ተሸሞ ፵ ዓመት አገልግሎ ግንቦት ፳፯ ቀን ዐርፏል

በሞተ በ፬ኛው ቀን ያስነሣው አልዓዛርን በ፬ኛው ቀን በዕለተ ረቡዕ እናከብረው ዘንድ የዕለቱ ስያሜ አልዓዛር ተብሏል።

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤
በዐቢይኀይል ወሥልጣን፤
አሰሮ ለሰይጣን፤
አግዓዞ ለአዳም፤
ሰላም፤
እምይእዜሰ፤
ኮነ
ፍሥሐ ወሰላም።

በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን? 1ኛ ሳሙ 15፥ 32። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን በሰማሁ ጊዜ እጅግ ከባድ ሀዘን ተሰማኝ። በረከታቸው ይደርብን። ብፁዕ ወቅ...
26/01/2026

በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን? 1ኛ ሳሙ 15፥ 32።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን በሰማሁ ጊዜ እጅግ ከባድ ሀዘን ተሰማኝ። በረከታቸው ይደርብን።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ዕንባቆም ነገ ጥር 19/2018 ዓ.ም በተማሩበት፣ ባደጉበት፣ ደፋ ቀና ባሉበትና በመነኮሱበት እንዲሁም ለረጅም ዘመናት ባገለገሉበት በታላቁ ደብር በደብረ ሊባኖስ ገዳም ሥርዓተ ቀብራቸው ይፈጸማል። በረከታቸው አይለየን።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tora ቶራ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share